top of page

ኤፍሬም ፡ አለሙ

Mezmur

  1. ክብራችን ፡ አንተ 

  2. የጌታ ፡ ልጅ

  3. ተይ ፡ ነፍሴ

  4. ሲጀምር ፡ በቅባት

  5. ትርፌማ ፡ ቅባት ፡ ነው

  6. እረኛዬ

  7. ከአንተ ፡ ጋር

  8. ካልባረከኝ

  9. ርዕስ

  10. አልችልበትም

  11. አስታዋሼ

  12. ዘምር ፡ አለኝ

  13. ክንዱ ፡ ነው

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ     1

ክብራችን ፡ አንተ

ክብራችን ፡ አንተ ፡ ዝርግፍ ፡ ጌጣችን
ውበታችን ፡ ነህ ፡ ጌታ ፡ አባታችን
በጨለማ ፡ ላይ ፡ የምታበራ
የንጋት ፡ ኮከብ ፡ አንተ ፡ ነህና ፡ ከፍ ፡ በል

የይሁዳ ፡ አንበሳ ፡ ሞትን ፡ ገዳይ
የዳዊት ፡ ዘር ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ኤልሻዳይ
ሲኦልን ፡ ድል ፡ ነስተህ ፡ ቀንበር ፡ ሰባሪ
ዘራችን ፡ ይሁን ፡ ለአንተ ፡ ዘማሪ :ከፍ በል

የአንተ ፡ በመሆኔ ፡ ኮራሁኝ ፡ እኔ
የእኔ ፡ ነህ ፡ ሲለኝ ፡ ደስ ፡ ደስ ፡ አለኝ (፪x)

አዝ፦ አይቻለሁ (ሆ) ፡ በምድር ፡ ላይ (ሆ)
የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ጥግ ፡ የበላይ
ሁሉም ፡ ገደብ ፡ ልክ ፡ አለው
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ብቻ ፡ አቻ ፡ የሌለው
አቻ ፡ የሌለው (፫x) ፡ ኢየሱስ ፡ ነው
ወደር ፡ የሌለው (፫x) ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

ምድር ፡ አልቻለችም ፡ አለቃዋን ፡ ይዛ
መልሳ ፡ ተፋችው ፡ ፈጣሪዋን ፡ ታዛ
ዓለምና ፡ ሰይጣን ፡ ሲዖል ፡ ያልቻለው
የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አቻ ፡ የሌለው

አቻ ፡ የሌለው ፡ ወደር ፡ የሌለው
ኢየሱስዬ ፡ ብቻ ፡ ሞት ፡ ያልበገረው
አቻ ፡ የሌለው ፡ ወደር ፡ የሌለው (፪x)

አዝ፦ አይቻለሁ (ሆ) ፡ በምድር ፡ ላይ (ሆ)
የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ጥግ ፡ የበላይ
ሁሉም ፡ ገደብ ፡ ልክ ፡ አለው
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ብቻ ፡ አቻ ፡ የሌለው
አቻ ፡ የሌለው (፫x) ፡ ኢየሱስ ፡ ነው
ወደር ፡ የሌለው (፫x) ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

እግሩ ፡ እንደ ፡ ጋለ ፡ ናስ ፡ ዐይኖቹ ፡ ነበልባል ፡ ነው
እርሱን ፡ ተመልክቶ ፡ የሚቆም ፡ ሰው ፡ ማነው
ስንቱ ፡ ጀግና ፡ ሞቶ ፡ መቃብር ፡ ሲቀር
ኢየሱስ ፡ ተነስቷል ፡ አርጓል ፡ በክብር

ንጉሠ ፡ ነገሥት ፡ ነው ፡ ያለ ፡ የነበረ
ወደፊትም ፡ ይኖራል ፡ ገና ፡ እየከበረ
እየተከበረ ፡ ገና ፡ እየከበረ (፪x)

ክብራችን ፡ አንተ ፡ ዝርግፍ ፡ ጌጣችን
ውበታችን ፡ ነህ ፡ ጌታ ፡ አባታችን
በጨለማ ፡ ላይ ፡ የምታበራ
የንጋት ፡ ኮከብ ፡ አንተ ፡ ነህና ፡ ከፍ ፡ በል

የይሁዳ ፡ አንበሳ ፡ ሞትን ፡ ገዳይ
የዳዊት ፡ ዘር ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ኤልሻዳይ
ሲኦልን ፡ ድል ፡ ነስተህ ፡ ቀንበር ፡ ሰባሪ
ዘራችን ፡ ይሁን ፡ ለአንተ ፡ ዘማሪ : ከፍ:በል

የአንተ ፡ በመሆኔ ፡ ኮራሁኝ ፡ እኔ
የእኔ ፡ ነህ ፡ ሲለኝ ፡ ደስ ፡ ደስ ፡ አለኝ (፪x)

አዝ፦ አይቻለሁ (ሆ) ፡ በምድር ፡ ላይ (ሆ)
የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ጥግ ፡ የበላይ
ሁሉም ፡ ገደብ ፡ ልክ ፡ አለው
የእኔ ፡ ጌታ ፡ ብቻ ፡ አቻ ፡ የሌለው
አቻ ፡ የሌለው (፫x) ፡ ኢየሱስ ፡ ነው
ወደር ፡ የሌለው (፫x) ፡ ኢየሱስ ፡ ነው

የዚህ ፡ ዓለም ፡ ገዢ ፡ ሲፎክር ፡ ሲያቅራራ
ገደልኩት ፡ ቀበርኩት ፡ እያለ ፡ ሲያወራ
በትንሳኤው ፡ ጉልበት ፡ ኢየሱስ ፡ ተነሳ
ጠላቴም ፡ ወደቀ ፡ በይሁዳ ፡ አንበሳ

ሰባቱን ፡ ማህተም ፡ ቋጠሮን ፡ የፈታ
ኢየሱስ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ የይሁዳ ፡ አንበሳ (፫x)
የይሁዳ ፡ አንበሳ ፣ የይሁድ ፡ አንበሳ (፪x)

ለክብሩ (ሆ) ፡ ለኃይሉ (ሆ)
ቢዘመር (ሆ) ፡ ለስሙ (ሆ)
ቢወራ ፡ በምድር ፡ አይበቃም ፡ ለእግዚአብሔር
ለእግዚአብሔር (፫x) ፡ አለኝ ፡ ዘምር
ለእግዚአብሔር (፫x) ፡ አለኝ ፡ ዘምር

"ሃሌሉያ ፡ እሰይ ፡ ኢየሱስ
ኢየሱስ ፡ አቻ ፡ የለውም"

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ      2

የጌታ ፡ ልጅ

የጌታ ፡ የጌታ ፡ ልጅ
የኢየሱስ ፡ ልጅ ፡ ቀና ፡ በል ፡ እንጂ
የአባቴ ፡ የአምላኬ ፡ ልጅ
የኢየሱስ ፡ ልጅ ፡ ኮራ ፡ በል ፡ እንጂ

ጠላት ፡ ሲቆዝም ፡ ያቀርቅር ፡ እንጂ
ቀና ፡ ቀና ፡ በል ፡ የጌታ ፡ ልጅ
እርሱን ፡ ለፈራው ፡ ላከበረው
እስከ ፡ ሺህ ፡ ትውልድ ፡ በረከት ፡ ነው
ጌታን ፡ ተማምኖ ፡ የለም ፡ ዝምታ
በእርግጥ ፡ ተሰብሯል ፡ ይመለክ ፡ ጌታ

ከዚህ ፡ በፊት ፡ የለመድኩት
የጠየኩት ፡ ያሳየሁት ፡ ነገር (፪x)
ዞሮ ፡ ገባ ፡ እጄ ፡ ገባ
አልቀረብኝ ፡ እግዚአብሔር ፡ ሲናገር ፡ ነገር
ዙፋኑ ፡ ስር ፡ መቅደሱ ፡ ስር
ማደሪያው ፡ ስር ፡ ስለምነው ፡ ውዬ (፪x)
አላፈርኩም ፡ አልከሰርኩም ፡ 
ተሳካልኝ ፡ ጌታ ፡ ጌታን ፡ ብዬ (፪x)

ብዬማ ፡ ጌታ ፡ አለ ፡ ብዬ
ብዬማ ፡ ታለምአልኜ
ብዬማ ፡ ነገር ፡ ተሳካ
ብዬማ ፡ እርሱን ፡ ለምኜ

የኢየሱስ ፡ ውለታው ፡ የበዛባችሁ
ቅኔን ፡ ተቀኙለት ፡ እልል ፡ ብላችሁ
ለክብሩ ፡ የሚሆን ፡ አምጡ ፡ ምሥጋና
እስቲ ፡ ጨምሩለት ፡ ቅዱስ ፡ ነውና

ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ የምን ፡ ዝምታ
ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ ከበሮ ፡ ይመታ
ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ ሳመልከው ፡ ውዬ
ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ ሳመልከው ፡ ይነጋ

የጌታ ፡ የጌታ ፡ ልጅ
የኢየሱስ ፡ ልጅ ፡ ቀና ፡ በል ፡ እንጂ
የአባቴ ፡ የአምላኬ ፡ ልጅ
የኢየሱስ ፡ ልጅ ፡ ኮራ ፡ በል ፡ እንጂ

መንግሥተ ፡ ሠማይ ፡ የጀግና ፡ አገር
የእኛም ፡ አገር ፡ ነች ፡ በዚያ ፡ እንድንኖር
በምድር ፡ መቶ ፡ እጥፍ ፡ በላይ ፡ ደስታ
ትልቅ ፡ ዕድል ፡ ነው ፡ መሆን ፡ የጌታ
አክሊል ፡ ያገኛል ፡ ድል ፡ ያነሳው
ለእግዚአብሔር ፡ ኖሮ ፡ የጨረሰው

ኢየሱሴን ፡ ተቀብሎ
. (1) . ጌታ ፡ ንጉሥ ፡ ያደረገውን ፡ ሰውን
እንደ ፡ እርሱ ፡ የለም ፡ የታደለ
ምስጉን ፡ ትውልድ ፡ ከሞት ፡ ያዳነው ፡ ሰው
ውኃው ፡ ተባርኮለት
ደዌ ፡ ችግር ፡ ተወግዶለት ፡ ሞትን
ተዘልሎ ፡ ተቀምጧል
እንደ ፡ አንበሳ ፡ አርፏል ፡ በድፍረት ፡ ሕይወት

እርሱማ ፡ ያመስግነው
እርሱማ ፡ ባለ ፡ ዕዳ ፡ ነው
እርሱማ ፡ ማቁ ፡ ተቀዶ
እርሱማ ፡ ሊዘምረው

የኢየሱስ ፡ ውለታው ፡ የበዛባችሁ
ቅኔን ፡ ተቀኙለት ፡ እልል ፡ ብላችሁ
ለክብሩ ፡ የሚሆን ፡ አምጡ ፡ ምሥጋና
እስቲ ፡ ጨምሩለት ፡ ቅዱስ ፡ ነውና

ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ የምን ፡ ዝምታ
ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ ከበሮ ፡ ይመታ
ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ ሳመልከው ፡ ውዬ
ደግሞ ፡ ለጌታ ፡ ሳመልከው ፡ ይነጋ

እርሱማ ፡ ያመስግነው
እርሱማ ፡ ባለ ፡ ዕዳ ፡ ነው
እርሱማ ፡ ማቁ ፡ ተቀዶ
እርሱማ ፡ ሊዘምረው

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       3

ተይ ፡ ነፍሴ

አዝ፦ ተይ ፡ ነፍሴ
የአምላክሽን ፡ ቃል ፡ ስሚና
ግራ ፡ ቀኙን ፡ ተይውና
ኋላ ፡ ደግሞ ፡ እንዳይቆጭሽ
ከአምላክሽ ፡ ጋር ፡ ተጣልተሽ
እርሱ ፡ ነው ፡ ሚረባሽን ፡ ሚያውቅልሽ
ከእርሱ ፡ ሌላ ፡ አትፈልጊ ፡ የሚረባሽን

አሃሃ ፡ አምላክሽ ፡ አለ ፣ አሃሃ ፡ ሚያስብልሽ
አሃሃ ፡ ግራና ፡ ቀኙን ፣ አሃሃ ፡ ምን ፡ አሳየሽ
አሃሃ ፡ እርሱስ ፡ ስለአንቺ ፣ አሃሃ ፡ ቆስሏልና????
አሃሃ ፡ ሌላ ፡ አትፈልጊ ፣ አሃሃ ፡ አይጠቅምምና

ኤሄ ፡ ሞልቶ ፡ ላይሞላ
ኤሄ ፡ ለዓለም ፡ ነገር
ነፍሴ ፡ አትጨነቂ ፡ የቀረው ፡ ይቅር
ኤሄ ፡ ሁሉ ፡ ከንቱ ፡ ነው
ኤሄ ፡ የከንቱ ፡ ከንቱ
ነፍሴ ፡ ቃሉ ፡ ይሻላል ፡ የእርሱ ፡ የአንደበቱ

እኔ ፡ ደግሞ ፡ ወይ ፡ ለራሴ
ቀን ፡ አስቦ??? ፡ ለክብር ፡ ነፍሴ
የሰጠኀኝ ፡ ፈራሽ ፡ ሥጋዬ
ላይሆነኝ ፡ መከበሪያዬ
አባትዬ ፡ ባክህ ፡ አደራ
በዘመኔ ፡ ስራህን ፡ ልስራ
አስከብሬህ ፡ ልኑር ፡ ለክብርህ
ስምህ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ እንዲጠራ

አዝ፦ ተይ ፡ ነፍሴ
የአምላክሽን ፡ ቃል ፡ ስሚና
ግራ ፡ ቀኙን ፡ ተይውና
ኋላ ፡ ደግሞ ፡ እንዳይቆጭሽ
ከአምላክሽ ፡ ጋር ፡ ተጣልተሽ
እርሱ ፡ ነው ፡ ሚረባሽን ፡ ሚያውቅልሽ
ከእርሱ ፡ ሌላ ፡ አትፈልጊ ፡ የሚረባሽን

አሃሃ ፡ አታስጨንቂኝ ፣ አሃሃ ፡ አታውኪኝ
አሃሃ ፡ ወዲህና ፡ ወዲያ ፣ አሃሃ ፡ አትበይቢኝ
አሃሃ ፡ የዓለም ፡ ብልጭልጭ ፣ አሃሃ ፡ መልኩ ፡ ውበቱ
አሃሃ ፡ ሁሉም ፡ ጠፊ ፡ ነው ፣ አሃሃ ፡ ደርሷል ፡ ሰዓቱ

ኤሄ ፡ ኀጢአት ፡ ብትሰሪ
ኤሄ ፡ ትሞቻለሽ
ነፍሴ ፡ ጽድቅን ፡ ብትሰሪ
በሕይወት ፡ ትኖሪያለሽ
ኤሄ ፡ እንዳያዝንብሽ
ኤሄ ፡ የሞተልሽን
ነፍሴ ፡ ለጽድቅ ፡ ንቂ
በሕይወት ፡ ለሚያኖርሽን

ሥጋ ፡ ነቅቶ ፡ መንፈስ ፡ ቢደክም
መንፈስ ፡ ነቅቶ ፡ ሥጋ ፡ ሲደክም
ለበረታው ፡ ላሸነፈው ፡ ብትወግኚ ፡ ለበለጠው
ነፍሴ ፡ ዕውቀት ፡ ፍቃድ ፡ አለሽ
ተገዢለት ፡ ለታደገሽ
ለግዚአብሄር ፡ ለስሙ ፡ ኑሪ
በሰማይ ፡ ቤት ፡ ፊቱ ፡ እንዳታፍሪ

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       4

ሲጀምር ፡ በቅባት

ሲጀምር ፡ በቅባት ፡ ሲያልቅም ፡ በቅባት
እግዚአብሔር ፡ ስላለ ፡ የኃያላን ፡ አባት
አይወድቁም ፡ አንወድቅም ፡ ከዛሬ ፡ ጀምሮ
ገና ፡ ይነሳሉ ፡ ቅባቱን ፡ ጨምሩ ፡ መንፈሱን ፡ ጨምሩ

ጨመረብኝ ፡ ቅባቱ ፡ ጨመረብኝ
ወረደብኝ ፡ መንፈሱ ፡ ፈሰሰብኝ
እግዚአብሔር ፡ በክብር ፡ በበቀል ፡ አስነሳኝ
ጨመረብኝ ፡ ቅባቱ ፡ ጨመረብጭ
በአዳዲስ ፡ ዝማሬ ፡ በምሥጋና ፡ ሞላኝ
ጨመረብኝ ፡ ቅባቱ ፡ ጨመረብጭ
እግዚአብሔር ፡ በክብር ፡ በበቀል ፡ አስነሳኝ
ጨመረብኝ ፡ ቅባቱ ፡ ጨመረብጭ
በአዳዲስ ፡ ዝማሬ ፡ በምሥጋና ፡ ሞላኝ

ኤልያስን ፡ ሳይቀር ፡ ያስፈራራችው
ናቦትን በርስቱ ፡ በርስቱ ፡ ያስገደለችው (፪x)
አረፍን ፡ ዘንድሮ ፡ እዩ ፡ ተቀብቷል
ኤልዛቤልን ፡ ከላይ ፡ ይፈጠፍጣታል ፡ ውሾች ፡ ይበሏታል

ጉድ ፡ ፈላባት ፡ ኤልዛቤል ፡ ጉድ ፡ ፈላባት

ጉድ ፡ ፈላባት ፡ ኤልዛቤል ፡ ጉድ ፡ ፈላባት
እንዲህ ፡ አትቀጥልም ፡ እንዳማረባት
ጉድ ፡ ፈላባት ፡ ኤልዛቤል ፡ ጉድ ፡ ፈላባት
ድንገት ፡ ሳታስበው ፡ እዩ ፡ ተነሳባት (፪x) [1]

ዓይኑ ፡ አረፈብኝ ፡ ወዳጄ (፬x)
ከሰዉ ፡ መሃል ፡ ሲያደላ ፡ ለእኔ ፡ አየሁት ፡ በዐይኔ (፪x)
ተሸክሞኛል ፡ በንስር ፡ ክንፍ
እንደ ፡ እናትም ፡ አባትም ፡ ሆነልኝ (፪x) ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ
የእንደገና ፡ አምላክ ፡ እንደገናዬ
በእጅህ ፡ መዳፍ ፡ ቀረጽከኝ (፪x) ፡ ሆንከኝ ፡ ጌታዬ

ጌታዬ (፪x) (ባለውለታዬ)
ኢየሱስ ፡ ጌታዬ (ሆንከኝ ፡ ጥላዬ)

ጐልያድ ፡ ሚባለው ፡ የውጊያ ፡ ጦረኛ
አርባ ፡ ቅን ፡ ሲፎክር ፡ ህዝቡን ፡ አልስተኛም (፪x)
ይፎክር ፡ ዝም ፡ በሉት ፡ ዳዊት ፡ እስኪመጣ
በጠጠር ፡ ይወድቃል ፡ የማታ ፡ የማታን ፡ የማታ ፡ የማታ [2]

የማታ ፡ የማታ ፡ ድሉ ፡ የጌታ ፡ ነው ፡ የማታ ፡ የማታ (፪x)
ተሸክሞኛል ፡ በንስር ፡ ክንፍ
እንደ ፡ እናትም ፡ አባትም ፡ ሆነልኝ (፪x) ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ
የእንደገና ፡ አምላክ ፡ እንደገናዬ
በእጅህ ፡ መዳፍ ፡ ቀረጽከኝ (፪x) ፡ ሆንከኝ ፡ ጌታዬ

ጌታዬ (፪x) (ባለውለታዬ)

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       5

ትርፌማ ፡ ቅባት ፡ ነው

ሥምህ ፡ በአፌ ፡ ላይ ፡ ይጣፍጠኛል
ሁሌ ፡ ስጠራው ፡ ደስ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
የትኛው ፡ ሥም ፡ ነው ፡ የተወደደው
ጠዋት ፡ ተወርቶ ፡ ማታ ፡ የሚወርደው
እንዳየነው

የእኔ ፡ ኢየሱስ ፡ ግን ፡ ሥሙ ፡ ይለያል
ሁሌ ፡ ስጠራው ፡ ደስ ፡ ደስ ፡ ይለኛል
ጠረነ ፡ ልዩ ፡ ማዕዛ ፡ ያለው
የአባትዬ ፡ ሥም ፡ ልክ ፡ እንደ ፡ ማር ፡ ነው
እንደ ፡ ማር

እንደ ፡ ማር ፡ ኧረ ፡ እንደ ፡ ማር (፬x)

እኔስ ፡ ቆርጫለሁ ፡ ለጌታ ፡ ዘንድሮ
ሕይወት ፡ ተገለጠ ፡ በራልኝ ፡ በቶሎ
ዋጋዬን ፡ ተምኜ ፡ ስለወጣሁኝ
እመቅደሱ ፡ ደጃፍ ፡ ወስዳችሁ ፡ ጣሉኝ

ትርፌማ ፡ ቅባት ፡ ነው ፡ ቅባት ፡ በመንገዴ
ያገኘኛል ፡ አልኩኝ ፡ ያየኛል ፡ አባቴ
ዋጋዬን ፡ ተምኜው ፡ ስለወጣሁኝ
እመቅደሱ ፡ ደጃፍ ፡ ወስዳችሁ ፡ ጣሉኝ (፫x)

አሄ ፡ ኦሆ

አርዶ ፡ የወጣ ፡ ሰው ፡ ከቶ ፡ አይመለስም
ጌልጌላ ፡ ተነስቶ ፡ ቤቴል ፡ ላይ ፡ አይቆምም
እያሪኮን ፡ አልፎ ፡ ዮርዳኖስ ፡ ይዘልቃል
እጥፍ ፡ መንፈስ ፡ ይዞ ፡ በክብር ፡ ይመለሳል

በኤልያስ ፡ እጅ ፡ ላይ ፡ ውኃ ፡ የሚያፈሰው
አስራ ፡ ሁለት ፡ ጥማድ ፡ በሬ ፡ አረደው
በሕያው ፡ ልብሱ ፡ ምን ፡ አለ ፡ የተከተለው
ሞኝ ፡ ሆኖ ፡ አይደለም ፡ ክብር ፡ አይቶ ፡ ነው
ቅባት ፡ አይቶ ፡ ነው ፡ ክብር ፡ አይቶ ፡ ነው

ጌልጌላ ፡ ሸለፈትክ ፡ የተገረዘው
ቤቴል ፡ የእግዚአብሔር ፡ ቤት ፡ የተጸለየው
እያሪኮም ፡ ይናድ ፡ በጩኸት ፡ ይፍረስ
ዮርዳኖስ ፡ ልጠመቅ ፡ በመንፈስ ፡ ቅዱስ

አባናና ፡ ፋርፋን ፡ አልል ፡ እንደ ፡ ሰው
ዮርዳኖስ ፡ ይበልጣል ፡ የደፈረሰው
ብቅ ፡ ትልቅ ፡ ብዬል ፡ ከለምጽ ፡ እነጻለሁ
አንተ ፡ ያልከኝ ፡ ቦታ ፡ ፈውስ ፡ አገኛለሁ (፪x)
መዳን ፡ አገኛለሁ

ዘመኔ ፡ እንደ ፡ ሻማ ፡ እንደ ፡ ጧፍ ፡ ቢነድ
ያንስበታል ፡ እንጂ ፡ መች ፡ ይበዛበት
እርሱማ ፡ ተዋርዶ ፡ በሞቱ ፡ አክብሮኝ
ለኢየሱሴ ፡ ኖሬ ፡ እስቲ ፡ ይለይልኝ

አሸፈተው ፡ ልቤን ፡ ኢየሱስን ፡ ወዶ
የሠማይ ፡ አስባለኝ ፡ የምድሩን ፡ አስንቆ
ልቤ ፡ ትዝታዬም ፡ እርሱ ፡ ጋር ፡ ቀረና
ሁሉንም ፡ አሳቀኝ ፡ የእርሱ ፡ በለጠና
ክብር ፡ በለጠና ፡ ቅባት ፡ በለጠና

ሞኝ ፡ ነህ ፡ ይሉኛል ፡ የታል ፡ ሞኝነቴ
አተረፈኩኝ ፡ እንጂ ፡ ምንድን ፡ ነው ፡ ጉዳቴ
ኢየሱስን ፡ ይዤ ፡ እኔስ ፡ አትርፊያለሁ
ምድር ፡ ተቀምጬ ፡ ቤቴ ፡ በሠማይ ፡ ነው

ይኸውልህ ፡ ልቤን ፡ እንካ ፡ ውሰደው
አንተ ፡ ጋር ፡ ይቀመጥ ፡ የእኔ ፡ ከንቱ ፡ ነው
ሁሉንም ፡ ሰብስቤ ፡ ለአንተ ፡ ሰጠሁና
አንተን ፡ አንተን ፡ አልኩኝ ፡ የአንተ ፡ በለጠና
መንፈስ ፡ በለጠና ፡ ቅባት ፡ በለጠና

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       6

እረኛዬ

አዝ፦ እረኛዬ (፪x) ፡ ነህ
እረኛዬ ፡ ነህ ፡ የነፍሴ ፡ ጠባቂን
ከአንበሳና ፡ ከድብ ፡ ከአውሬው ፡ ከነጣቂ

ያ ፡ ዳዊት ፡ እውነቱን ፡ እኮ ፡ ነው
ኧረኛዬ ፡ ብሎ ፡ የዘመረው
ከአንበሳ ፡ ከድብ ፡ ስታተርፈው
ያለአንተ ፡ ማን ፡ አስተዋሽ ፡ አለው
ገበታን ፡ አዘጋጀህለት
ንግስናን ፡ አንተው ፡ ስታነግሰው
ባይዘምር ፡ ይገርመኝ ፡ ነበር
የእኔም ፡ ታሪክ ፡ እንደዳዊት ፡ አለ

አባትዬ ፡ አባብዬ ፡ ነህ
አባትዬ ፡ ነህ ፡ የነፍሴ ፡ ጠባቂን
ከአንበሳና ፡ ከድብ ፡ ከአውሬው ፡ ከነጣቂ

መሰማሪያን ፡ ከአገኘሁ ፡ ቆየው
እረኛዬን ፡ ስለተጠጋሁ
በክንፎቹ ፡ ጥላ ፡ ስር ፡ ሆኜ
እኖራለሁ ፡ ተደላድዬ

(ለምን ፡ ቢባል) እረኛዬን ፡ ይዤ
(ለምን ፡ ቢባል) ቅጥሩን ፡ እዘላለሁ
(ለምን ፡ ቢባል) ሓሩሩ ፡ እንዳይጐዳኝ
(ለምን ፡ ቢባል) ጥላን ፡ አግኝቻለሁ (፪x)

አዝ፦ እረኛዬ (፪x) ፡ ነህ
እረኛዬ ፡ ነህ ፡ የነፍሴ ፡ ጠባቂን
ከአንበሳና ፡ ከድብ ፡ ከአውሬው ፡ ከነጣቂ

ከሰማይ ፡ ወደቀብኝ ፡ እጣ
እንዳትል ፡ ልዘምር ፡ ለጌታ
ጥሪ ፡ ነው ፡ የእርሱ ፡ ያደረገኝ
ለሌላው ፡ መሆን ፡ አቃተኝ
ከእናቴ ፡ ማህፀን ፡ ጀምሮ
የለየኝ ፡ ዘማሪ ፡ ነህ ፡ ብሎ
ዕድሜዬን ፡ ለእርሱ ፡ ሰጥቻለሁ
ሳመልከው ፡ ስዘምር ፡ እኖራለሁ

አባትዬ ፡ አባብዬ ፡ ነህ
አባትዬ ፡ ነህ ፡ የነፍሴ ፡ ጠባቂን
ከአንበሳና ፡ ከድብ ፡ ከአውሬው ፡ ከነጣቂ

ቸርነቱና ፡ ምህረቱ ፡ ሁልጊዜ ፡ ይከተሉኛል
በእግዚአብሔር ፡ ቤት ፡ ለዘላለም
እኖራለሁ ፡ ምን ፡ ያስፈራኛል

(እኔ ፡ አልፈራም) በትሩ ፡ ምርኩዞ
(እኔ ፡ አልፈራም) እነርሱ ፡ ያጽናኑኛል
(እኔ ፡ አልፈራም) ከፊቴ ፡ ገበታ
(እኔ ፡ አልፈራም) ተዘጋጅቶልኛል
(እኔ ፡ አልፈራም) ጽዋዬማ ፡ እርሱ ፡ ዘንድ
(እኔ ፡ አልፈራም) የተረፈ ፡ ነው
(እኔ ፡ አልፈራም) ኢየሱስን ፡ ይዤ
(እኔ ፡ አልፈራም) ምን ፡ እሆናለሁ

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       7

ከአንተ ፡ ጋር

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ልኑር ፡ አንተ ፡ ጋር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ኢየሱስ ፡ ልኑር ፡ አንተ ፡ ጋር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ያለ ፡ አንተ ፡ አይሆንልኝም ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ብቻዬን ፡ አያምርብኝ ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልበላ ፡ እጠግባለሁ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)

በንጉሥ ፡ ጮማ ፡ ከኖሩ ፡ ቆሎ ፡ ቆርጥመው ፡ ያደሩ
አስር ፡ እጅ ፡ አማረባቸው ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ የወገኑ
በምድር ፡ ተጨምጭቦልኝ ፡ በሰማይ ፡ ከምታፍርብኝ
ይቅርብኝ ፡ ሁሉም ፡ ይቅር ፡ ከአንተ ፡ ጋራ ፡ ብቻ ፡ ልኑር

መራብን ፡ አውቃለሁ ፡ መጥገብን
ማግኘትን ፡ አውቃለሁ ፡ ማጣትን
እኔ ፡ ማይሆንልኝ ፡ ማያምርብኝ
ያላንተ ፡ መኖር ፡ ነው ፡ የታውቅክልኝ
ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልበላ ፡ እጠግባለሁ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)

አዝ፦ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ልኑር ፡ አንተ ፡ ጋር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ኢየሱስ ፡ ልኑር ፡ አንተ ፡ ጋር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ያለ ፡ አንተ ፡ አይሆንልኝም ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ብቻዬን ፡ አያምርብኝ ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልበላ ፡ እጠግባለሁ ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልጠጣ ፡ ያረካኛል ፡ ከአንተ ፡ ጋር

ቢቃጠል ፡ ወጣትነቴ ፡ ቢነድም ፡ ለአንተ ፡ ጉልበቴ
ቢቀናም ፡ ክፉ ፡ ጠላቴ ፡ ለአንተ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አባቴ 
የሰው ፡ ልጅ ፡ ዕድሜ ፡ ሰንቃላ ፡ ሰማንያ ፡ አመት ፡ የማይሞላ
ድካም ፡ ነው ፡ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ አልሆንም ፡ እኔስ ፡ ተላላ

ሺህ ፡ ዓመት ፡ አልኖርም ፡ በምድር
እንደእንፋሎት ፡ ነው ፡ የሰው ፡ ልጅ ፡ ዘመን
በቃ ፡ ለአንተ ፡ ክብር ፡ ልኑርና
ዘመኔን ፡ ጨርሰው ፡ ጌታ ፡ ቀድስና
ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልበላ ፡ እጠግባለሁ ፡ ከአንተ ፡ ጋር (፪x)

ሙሴ ፡ አይቶ ፡ ብድራቱን ፡ የልጅ ፡ ልጅ ፡ ንግስናውን
ንቆታል ፡ ለእግዚአብሔር ፡ ብሎ ፡ አልጋውን ፡ ክብሩን ፡ ተምኖ
ኧረ ፡ ለእኔ ፡ ትልቅ ፡ እድል ፡ ነው ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ ብዬ ፡ ምኖረው
እንኳን ፡ አገልጋይ ፡ ሆኜ ፡ ይበቃል ፡ ባሪያ ፡ መባሌ

የእኔ ፡ መጨረሻ ፡ ጥግ ፡ እርካታዬ
መገኘትህ ፡ ሲኖር ፡ በቤት ፡ በጓዳዬ
ያን ፡ ጊዜ ፡ በፍፁም ፡ ልቤ ፡ ኧረካለሁ
ፊትህን ፡ እያየሁ ፡ ሁልጊዜ ፡ እጠግባለሁ

ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልበላ ፡ እጠግባለሁ ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ይሄ ፡ ልቤ ፡ ተመኝቶሃል ፡ ልኑር ፡ ከአንተ ፡ ጋር
ባልጠጣ ፡ ያረካኛል ፡ ከአንተ ፡ ጋር

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       8

 ካልባረከኝ

በረከት ፡ ፍለጋን ፡ ስንከራተት
እንዲያው ፡ በከንቱ ፡ አይ ፡ ስዋትት
ዛሬ ፡ ግን ፡ ገብቶኝ ፡ መጥቻለሁ
አንተን ፡ ከአገኘሁ ፡ ምን ፡ እሻለሁ

አዝ፦ ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)
ስሜን ፡ ቀይረህ ፡ ካልቀባኀኝ
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)
ልጄ ፡ ነህ ፡ ብለህ ፡ ካለወጥከኝ
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)

ሓሩሩ ፡ ኩሩ ፡ አቃጠለኝ
ደሞዜን ፡ ስንቴ ፡ ቀየረብኝ
ሽቅብ ፡ ስወጣ ፡ ቁልቁል ፡ ስወርድ
ዘመኔን ፡ ፈጀሁ ፡ በላባ ፡ ቤት

ቆይ ፡ ምን ፡ ያደርጋል ፡ ሃብት ፡ ቢበዛ
አንተ ፡ ከሌለህ ፡ ካልሆንከኝ ፡ ቤዛ
ሌሊቱ ፡ አቅላልቷል ፡ ሊነጋብኝ
እኔ ፡ አለቅህም ፡ ካልባረከኝ

ጌታ ፡ አድነኝ ፡ ለውጠኝ
ማለቴን ፡ አልተውም ፡ እስክትለውጠኝ
ጌታ ፡ አድነኝ ፡ ለውጠኝ
ጸሎቴን ፡ አልተውም ፡ እስክትለውጠኝ

በረከት ፡ ፍለጋን ፡ ስንከራተት
እንዲያው ፡ በከንቱ ፡ አይ ፡ ስዋትት
ዛሬ ፡ ግን ፡ ገብቶኝ ፡ መጥቻለሁ
አንተን ፡ ከአገኘሁ ፡ ወርሻለሁ???

አዝ፦ ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)
ስሜን ፡ ቀይረህ ፡ ካልቀባኀኝ
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)
ልጄ ፡ ነህ ፡ ብለህ ፡ ካለወጥከኝ
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)

የቅድስናን ፡ የጽድቅን ፡ ኑሮ
መኖር ፡ ፈልጌ ፡ ከአምናው ፡ ዘንድሮ
አመታት ፡ ዘመን ፡ ወሰደብኝ
መቼ ፡ ነው ፡ መጥተህ ፡ ምትቀይረኝ

እኔ ፡ አልፈልግም ፡ እንደዚህ ፡ ኑሮ
ተራራ ፡ መዞር ፡ አመታት ፡ ቆጥሮ
እስቲ ፡ አንድ ፡ እርምጃ ፡ ፈቀቅ ፡ አርገኝ
በክብርህ ፡ ልኑር ፡ አሳርፈኝ

ጌታ ፡ አድነኝ ፡ ለውጠኝ
ማለቴን ፡ አልተውም ፡ እስክትለውጠኝ
ጌታ ፡ አድነኝ ፡ ለውጠኝ
ጸሎቴን ፡ አልተውም ፡ እስክትለውጠኝ

አዝ፦ ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)
ስሜን ፡ ቀይረህ ፡ ካልቀባኀኝ
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)
ልጄ ፡ ነህ ፡ ብለህ ፡ ካለወጥከኝ
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም ፣ ካልዳሰስከኝ ፡ አልተውህም (፪x)

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       9

ርዕስ

እረጅሙን ፡ ጐዳና ፡ በጽድቅ ፡ እንዳልሄድኩኝ
አንተን ፡ እንዳላሳዝን ፡ ፊትህ ፡ እንደማልኩኝ
ዛሬ ፡ ምነው ፡ ጠፋኝ ፡ አቅም ፡ አጣን

እኔ ፡ ነኝ ፡ ጥፋተኛ ፡ እኔን ፡ እኔን ፡ ማረኝ
ዕንቁዬን ፡ ሜዳ ፡ ጥዬው ፡ ብቻዬን ፡ ቀረሁኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ መልሰኝ ፡ ምህረት ፡ አድርግልኝ

አዝ፦ መልሰኝ ፡ ወደድሮዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወዳስተማርከኝ
መልሰኝ ፡ ወደጓዳዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወደነገርከኝ
አንተን ፡ ተጣልቼ ፡ እንዴት ፡ እሆናለሁ
ከአንተ ፡ ተስማምቼ ፡ እኔስ ፡ እኖራለሁ

ስታበይ ፡ ገሥጸኝ ፡፡ ሳጠፋ ፡ ቅጣኝ
መንፈስህን ፡ ከእኔ ፡ አትውሰድብኝ
አንተ ፡ ዝም ፡ ካልከኝ ፡ ምንስ ፡ ይውጠኛል
የአንተ ፡ ዝምታ ፡ እኮ ፡ አፍ ፡ አለው ፡ ያወራል

ብቻ ፡ ይሁን ፡ እንጂ ፡ የነገርከኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ያልከኝ
እኔስ ፡ ከሃሳብህ ፡ ጋር ፡ እስማማለሁ ፡ ይሁን ፡ እንዳልከኝ (፪x)

ብዙ ፡ የለፋሁበት ፡ ያከማቸሁት ፡ ሃብቴ
ከእጄ ፡ ላይ ፡ ተበተነ ፡ ሳላውቀው ፡ ከጥማቴ
የተቀደስኩለት ፡ ከዳኝ ፡ ማንነቴ
አወይ ፡ አለመታዘዝ ፡ አሻፈረኝ ፡ ማለቴ
አይረባህም ፡ ስትለኝ ፡ አንተን ፡ አለመስማቴ
ዛሬ ፡ ግን ፡ ገብቶኛል ፡ ??? ፡ አባቴ

አዝ፦ መልሰኝ ፡ ወደድሮዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወዳስተማርከኝ
መልሰኝ ፡ ወደጓዳዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወደነገርከኝ
አንተን ፡ ተጣልቼ ፡ እንዴት ፡ እሆናለሁ
ከአንተ ፡ ተስማምቼ ፡ እኔስ ፡ እኖራለሁ

ጴጥሮስ፡ ሓዋርያው ፡ አልክድህም ፡ ያለው
ዶሮ ፡ ሳይጮህ ፡ በፊት ፡ ሶስት ፡ ጊዜ ፡ ነው ፡ የካደው
ነገር ፡ ግን ፡ ምህረትህ ፡ እጅግ ፡ ስለበዛ
አስበህ ፡ ለወጥከው ፡ ሰው ፡ አደረከው ፡ ጌታ

ብቻ ፡ ይሁን ፡ እንጂ ፡ የነገርከኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ያልከኝ
እኔስ ፡ ከሃሳብህ ፡ ጋር ፡ እስማማለሁ ፡ ይሁን ፡ እንዳልከኝ (፪x)

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       10

አልችልበትም

ስለማልችል ፡ ያለ ፡ አንተ ፡ መኖር
አትሂድብኝ ፡ ባክህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ
እኔስ ፡ ያለ ፡ አንተ ፡ አልችልምና
ችላ ፡ አትበለኝ ፡ ክብሬን ፡ ክብሬ ፡ ነህና

አዝ፦ አልችልበትም ፡ እኔስ
አይሆንልኝም ፡ እኔስ
ያላንተ ፡ መኖር (፪x)

ዓይኔን ፡ በእጄ ፡ አልወጋም ፡ የጠራኝን ፡ ትቼ
እንዴት ፡ ነው ፡ ምኖረው ፡ ከአንተ ፡ ተለይቼ
ሌላው ፡ ሚመካበት ፡ አለው ፡ ብዙ ፡ ነገር
ለእኔ ፡ ግን ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ የመኖሬ ፡ ትርጉም

አዝ፦ አልችልበትም ፡ እኔስ
አይሆንልኝም ፡ እኔስ
ያለአንተ ፡ መኖር

ሲከብደኝ ፡ ብቸኝነቴ ፡ ሳዝን ፡ ስተክዝ ፡ በቤቲት
ቅዱሱን ፡ መንፈስ ፡ አልኩኝ ፡ እባክህ ፡ አትሂድብኝ

የሰው ፡ ጥማቱ ፡ ሌላ ፡ ነው
የኤኔ ፡ ግን ፡ አንድ ፡ ብቻ ፡ ነው
ያላንተ ፡ መኖር ፡ አልችልም
ለአፍታ ፡ እንኳን ፡ አትተወኝ

ስለማልችል ፡ ያለ ፡ አንተ ፡ መኖር
አትሂድብኝ ፡ ባክህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ
እኔስ ፡ ያለ ፡ አንተ ፡ አልችልምና
ችላ ፡ አትበለኝ ፡ ክብሬን ፡ ክብሬ ፡ ነህና

ሳኦል ፡ ምን ፡ ነክቶት ፡ ከሰረ
ለሥጋው ፡ ምቾት ፡ ስለአደረ
አጥፋልኝ ፡ ብለህ ፡ ስትልከው
ያማረውን ፡ ለኤራሱ ፡ አስቀረው

በሚያልፈው ፡ ነገር ፡ ተታሎ
በድፍረት ፡ ሲጓዝ ፡ አይ ፡ ብሎ
ድምጽህን ፡ ንቆ ፡ ሲወጣ
መንፈስህ ፡ ሸሽቶ ፡ ተቀጣ

አጥፋልኝ ፡ ያልከውን ፡ አጠፋዋለሁኝ
ሰዋልኝ ፡ ያልከውን ፡ እሰዋዋለሁኝ
ዝክሩን ፡ ከምድር ፡ ላይ
መንግሥቱን ፡ አፍርሼ
አስደስትሃለሁኝ ፡ ቃልህን ፡ ጠብቄ

አዝ፦ አልችልበትም ፡ እኔስ
አይሆንልኝም ፡ እኔስ
ያላንተ ፡ መኖር (፪x)

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       11

አስታዋሼ

ሰው ፡ የረሳኝን ፡ አስታወስከኝ
ከአመድ ፡ ከትቢያ ፡ ያነሳኀኝ
እኔም ፡ ስላየሁ ፡ ክንድህን
ጌታ ፡ ደራሽ ፡ ነህ ፡ ልበልህ (፪x)

(ደራሽ ፡ ነህ) ምድረ ፡ በዳውን ፤ (ደራሽ ፡ ነህ) ያሳለፍከኝ
(ደራሽ ፡ ነህ) ምንጭን ፡ አፍልቀህ ፡ አጠጣኀኝ
(ደራሽ ፡ ነህ) አንዴ ፡ ጠጥቼ ፤ (ደራሽ ፡ ነህ) እንዳልጠማ
(ደራሽ ፡ ነህ) ሕይወት ፡ ሆንክልኝ ፡ በሞት ፡ ከተማ
(ደራሽ ፡ ነህ) ጌታ ፤ (ደራሽ ፡ ነህ) ለእኔ
(ደራሽ ፡ ነህ) ውዴ ፤ ደራሽ ፡ ነህ ፡ ለእኔ

ቃል ፡ ሲወጣ ፡ ከሰማይ ፡ ማን ፡ ይቆማል ፡ ደጃፉ ፡ ላይ
(ማን ፡ ይቆማል ፡ ሄ ፡ ማን ፡ ይቆማል ፡ ደጃፉ ፡ ላይ)
በአንዲት ፡ ጀምበር ፡ ደረስክና ፡ አፌን ፡ ሞላህ ፡ በምሥጋና
(ማን ፡ ይቆማል ፡ ሄ ፡ ማን ፡ ይቆማል)
እንዳለፈው ፡ ታለፈ ፡ አበሳዬ ፡ ተረሳ
(ማን ፡ ይቆማል ፡ ሄ ፡ ማን ፡ ይቆማል ፡ ደጃፉ ፡ ላይ)
እኔም ፡ ዛሬ ፡ ወግ ፡ ደረሰኝ ፡ የአስታዋሼን ፡ ስሙን ፡ ላንሳ
(ማን ፡ ይቆማል ፡ ሄ ፡ ማን ፡ ይቆማል)

አዝ፦ አስታዋሼ ፡ የእኔ ፡ ኧረኛ
ሰው ፡ ሲረሳኝ ፡ አሰብከኛ
አስታዋሼ ፡ የእኔ ፡ ዳኛ
ሰው ፡ ሲረሳኝ ፡ አሰብከኛ (፪x)

ሰው ፡ የረሳኝን ፡ አስታወስከኝ
ከአመድ ፡ ከትቢያ ፡ ያነሳኀኝ
እኔም ፡ ስላየሁ ፡ ክንድህን
ጌታ ፡ ደራሽ ፡ ነህ ፡ ልበልህ (፪x)

(ደራሽ ፡ ነህ) ምድረ ፡ በዳውን ፤ (ደራሽ ፡ ነህ) ያሳለፍከኝ
(ደራሽ ፡ ነህ) ምንጭን ፡ አፍልቀህ ፡ አጠጣኀኝ
(ደራሽ ፡ ነህ) አንዴ ፡ ጠጥቼ ፤ (ደራሽ ፡ ነህ) እንዳልጠማ
(ደራሽ ፡ ነህ) ሕይወት ፡ ሆንክልኝ ፡ በሞት ፡ ከተማ
(ደራሽ ፡ ነህ) ጌታ ፤ (ደራሽ ፡ ነህ) ለእኔ
(ደራሽ ፡ ነህ) ውዴ ፤ ደራሽ ፡ ነህ ፡ ለእኔ

ኢየሱሴ ፡ ባታየኝ ፡ ማን ፡ ነበረ ፡ የሚያየኝ
(ማን ፡ ነበረ ፡ ቆይ ፡ ማን ፡ ነበረ ፡ የሚያየኝ)
ግራ ፡ ገብቶኝ ፡ ስንገላታ ፡ ደረስክልኝ ፡ የእኔ ፡ ጌታ
(ማን ፡ ነበረ ፡ ሄ ፡ ማን ፡ ነበረ)
እነዛ ፡ እጆች ፡ ይባረኩ ፡ እኔን ፡ አቅፈው ፡ ያሳደጉ
(ማን ፡ ነበረ ፡ ቆይ ፡ ማን ፡ ነበረ ፡ የሚያየኝ)
አደረግከኝ ፡ ሽቅርቅር ፡ ጠላት ፡ ይፈር ፡ ያቀርቅር
(ማን ፡ ነበረ ፡ ሄ ፡ ማን ፡ ነበረ)

አዝ፦ አስታዋሼ ፡ የእኔ ፡ እረኛ
ሰው ፡ ሲረሳኝ ፡ አሰብከኛ
አስታዋሼ ፡ የእኔ ፡ ዳኛ
ሰው ፡ ሲረሳኝ ፡ አሰብከኛ (፪x)

እንዴት ፡ አስታወስከው ፡ ያንን ፡ ሰው (፪x)
እንዴት ፡ አስታወስከው ፡ ያንን ፡ ሰው (፪x)
እንዴት ፡ አስታወስከው ፡ ያንን ፡ ሰው (፪x)
እንዴት ፡ አስታወስከው ፡ ያንን ፡ ሰው (፪x)

አዝ፦ አስታዋሼ ፡ የእኔ ፡ ኧረኛ
ሰው ፡ ሲረሳኝ ፡ አሰብከኛ
አስታዋሼ ፡ የእኔ ፡ ዳኛ
ሰው ፡ ሲረሳኝ ፡ አሰብከኛ (፪x)

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       12

ዘምር ፡ አለኝ

ጠላት ፡ የጻፈው ፡ የሞት ፡ ደብዳቤ
ተቀዶ ፡ ሳየው ፡ ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ (ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ)
ጠላቴን ፡ ጥሎ ፡ ስላሳየኝ
ልቤም ፡ በደስታ ፡ ዘምር ፡ አለኝ (ዘምር ፡ አለኝ)

አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ)
አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ)
ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ)
ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ)

ሸንጐ ፡ ሰብስቦብኝ ፡ መክሮብኛል ፡ ዝቶብኛል
ሰበብ ፡ ፈልጐብኝ ፡ ይዋጋኛል ፡ ይዞረኛል
የሚጠብቀኝ ፡ ስለማይተኛ ፡ እኔም ፡ አርፌ ፡ እስቲ ፡ ልተኛ
ዙሪያዬ ፡ ቢዞር ፡ ቢሽከረከረ ፡ እኔ ፡ እንደሆነ ፡ አለኝ ፡ ክብር
የተቀባ ፡ ሰው ፡ ሰልፉ ፡ ብዙ ፡ ነው
ነገር ፡ ግን ፡ ጌታ ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ ነው

አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ)
አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ)
ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ)
ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ)

የሲኦል ፡ በር ፡ ሲዘጋ ፡ ለእኔ ፡ ሌቱ ፡ ሲነጋ (ሲነጋ) ፡ ሲነጋ (ሲነጋ)
ጠላቴ ፡ ሲመሽበት ፡ ለማጁ ፡ ሰው ፡ በራለት ፡ ነጋለት (ነጋለት) ፡ በራለት (በራለት)
ደሙ ፡ ነው ፡ ምልክቴ ፡ አይገባም ፡ ሞት ፡ እቤቴ ፤ ከቤቴ (ከቤቴ) ፡ እቤቴ (ከቤቴ)
ያሳረገኝ ፡ ደሙ ፡ ነው ፡ ስለዚህ ፡ እዘምራለሁኝ ፡ ለጌታ (ለጌታ) ፡ በደስታ (በደስታ)

ምልክት ፡ አለብኝ ፡ የኢየሱስ ፡ ደም ፡ በግምባሬ
ይፈራኛል ፡ ጠላት ፡ ከቶ ፡ አይቀርብም ፡ በሰፈሬ
በአጠገቤ ፡ ሺ ፡ በቀኝ ፡ አስር ፡ ሺ ፡ እየጣለልኝ ፡ ሆንኩኝ ፡ ድል ፡ ነሺ
ዙሪያዬ ፡ ስሜ ፡ በደሙ ፡ ታጥሯል ፡ ቅዱስ ፡ መንፈሱ ፡ ይጠብቀኛል
በድል ፡ ወጥቼ ፡ በድል ፡ እገባለሁ ፡ የእኔ ፡ ከለላ ፡ የእሳት ፡ ቅጥር ፡ ነው

ጠላት ፡ የጻፈው ፡ የሞት ፡ ደብዳቤ
ተቀዶ ፡ ሳየው ፡ ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ (ደስ ፡ አለው ፡ ልቤ)
ጠላቴን ፡ ጥሎ ፡ ስላሳየኝ
ልቤም ፡ በደስታ ፡ ዘምር ፡ አለኝ (ዘምር ፡ አለኝ)

አዝ፦ ዘምር (፪x) (ዘምር ፡ አለኝ)
አምልክ (፪x) (አምልክ ፡ አለኝ)
ስገድ (፪x) (ስገድ ፡ አለኝ)
ለእርሱ ፡ ዘምር (ዘምር ፡ አለኝ)

ምህረቱ ፡ በዝቶብኝ ፡ በሕይወቴ ፡ አለሁኝ
የእኔ ፡ ነው ፡ የምለው ፡ ምንም ፡ ነገር ፡ የሌለኝ
በቃ ፡ ማርኮኛል ፡ ተማርኬያለሁ ፡ ለፍቅሩ ፡ ብዛት ፡ እጄን ፡ ሰጥቻለሁ
ከአሁን ፡ በኋላ ፡ የምኖረው ፡ ለጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ልስሙ ፡ ነው
ዕድሜ ፡ ቀጥሎ ፡ ኑር ፡ ስላለኝ ፡ እኔም ፡ ለስሙ ፡ እኖራለሁኝ

ኦሮምኛ (ኦሮምኛውን ፡ ግጥም ፡ ይጻፉልን)

Get in Touch

ኤፍሬም ፡ አለሙ       13

ክንዱ ፡ ነው

አዝ፦ ክንዱ ፡ ነው ፡ ታሪኬን ፡ የለዋወጠው
ጣቱ ፡ ነው ፡ ነገሬን ፡ የቀያየረው (፪x)

አይቻለሁ ፡ በአንተ
ሸለቆው ፡ ውኃ ሲሞላ
ጌታ ፡ ስትሆነኝ ፡ ከለላ (፪x)

አንገት ፡ እንድደፋ ፡ እንዳቀረቅር
ከሰው ፡ በታችን ፡ ሆኜ ፡ ነበር ፡ ምኞቱ
ጠላቴማ ፡ ሰው ፡ ለማድረግ ፡ ከንቱ ፡ አወይ ፡ ልፋቱ
የማመልከው ፡ ጌታ ፡ እጄን ፡ ያዘኝ
እንደገና ፡ አነሳኝ ፡ ዳግም ፡ አቆመኝ

ማነው ፡ ማነው ፡ ማነው ፡ ኧረ ፡ ማነው ፡ ማነው
ማነው ፡ ማነው ፡ ማነው ፡ እኮ ፡ ማነው ፡ ማነው
እሃሃሃ ፡ እግዚአብሔር ፡ እኮ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የደረሰው (፪x)

አዝ፦ ክንዱ ፡ ነው ፡ ታሪኬን ፡ የለዋወጠው
ጣቱ ፡ ነው ፡ ነገሬን ፡ የቀያየረው (፪x)

አይቻለሁ ፡ በአንተ
ሸለቆው ፡ ውኃ ሲሞላ
ጌታ ፡ ስትሆነኝ ፡ ከለላ (፪x)

በዚያ ፡ በጭንቅ ፡ ቀን ፡ በቁርጥ ፡ ጊዜ ፡ በመከራ ፡ ሰዓት
ከጐኔ ፡ የሚቆም ፡ አይዞህ ፡ የሚለኝ ፡ አጋዥ ፡ ባጣሁበት
የናዝሬቱ ፡ ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ሲመጣ
ጉልበቴም ፡ ከፍ ፡ አለልኝ ፡ አቅሜም ፡ በረታ

ማነው ፡ ማነው ፡ ማነው ፡ ኧረ ፡ ማነው ፡ ማነው
ማነው ፡ ማነው ፡ ማነው ፡ እኮ ፡ ማነው ፡ ማነው
እሃሃሃ ፡ እግዚአብሔር ፡ እኮ ፡ ነው
ለእኔ ፡ የደረሰው (፪x)

Get in Touch
  • facebook
  • twitter
  • linkedin

©2019 by My Site. Proudly created with Wix.com

bottom of page